ስንክሳር
7.32K subscribers
825 photos
4 videos
37 files
237 links
በስንክሳር channal ስንክሳሩ ተገልጦ ቅዱሳን ይዘከራሉ፣ ወቅቱን የጠበቁ መረጃዎችን ያገኛሉ፡፡ ይከታተሉን!
Download Telegram
✞✞✞ እንኩዋን ለካህኑ #ሰማዕት_አባ_ኦሪ ዓመታዊ
የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞✞✞
#ቅዱስ_አባ_ኦሪ_ቀሲስ "
ይህ ቅዱስ አባት የዘመነ ሰማዕታት ፍሬ ነው:: በዘመኑ
(በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን) #ክርስቲያን መሆን ብቻውን
ለሞት እንደሚያበቃ ወንጀል ይቆጠር ነበር:: በጊዜው
ክርስቲያን ከመሆን በባሰ መንገድ #እረኛ_ካህን ሆኖ
መገኘት በጣም ከባድ ነበር::
ከመነሻውም ያን ጊዜ ክህነት የሚሰጠው በሕዝቡና
በሊቀ ዻዻሱ ምርጫ ነበር እንጂ እንደ ዘንድሮ "እኔን ሹሙኝ" ማለት ልማድ አልነበረም:: ምዕመናንም
እረኛቸውን ሲመርጡ በጉቦ: በዝምድና አይደለም::
በርትቶ የሚያበረታቸውን: ለመንጋው ራሱን አሳልፎ
የሚሰጠውን ይመርጣሉ እንጂ::
ያልሆነ ሰው ለክህነት ቢመረጥ አንድም ክዶ ያስክዳል:
ሲቀጥልም ለሕዝቡ መሰናክል መሆኑ አይቀርም::
በጊዜው ( #በዘመነ_ሰማዕታት ) የነበሩ ካህናት የቤት
ሥራቸውም ማስተማር ብቻ አልነበረም:: በድፍረት
በምዕመናን ፊት አንገታቸውን ለሰይፍ መስጠት
ይጠበቅባቸው ነበር እንጂ::
ይህንን በገሃድ መፈጸም ከቻሉ አበው አንዱ ደግሞ አባ
ኦሪ ቀሲስ ናቸው:: ቅዱሱ ተወልደው ባደጉባት ሃገረ
#ስጥኑፍ (የግብጽ አውራጃ ናት) መጻሕፍትን የተማሩ:
ተወዳጅ እና ደግ ሰው ነበሩ::
አባ ኦሪ ገና ከወጣትነት ቀዳሚ ግብራቸው መንኖ
ጥሪት (ምናኔ) ነበር:: በንጽሕናቸው ደስ የተሰኙ
ምዕመናንም "ቅስና ተሹመህ ምራን: አስተምረን"
ቢሏቸው አበው ውዳሴ ከንቱን አይፈልጉምና "አይሆንም" አሉ::
ነገሩ ፈቃደ እግዚአብሔር ነበረና አባ ኦሪ ቅስናን ተሹመው ያገለግሉ ገቡ:: ሕዝቡን በማስተማር:
በመምከር: ደካማውን በማጽናት ብዙ ደክመዋል:: ከቅድስናቸው የተነሳ ቅዳሴ ሊቀድሱ ሲገቡ #ጌታችን በገሃድ ይገለጥላቸው ነበር:: ሠራዊተ መላእክትም
ከበው ይነጋገሯቸው ነበር::
#ሥጋውን_ደሙን በማቀበልም ተግተው ዘመናት
አለፉ:: ቆይቶ ግን ያ በዜና ይሰሙት የነበረ መከራ
( #ሰማዕትነት ) በደጃቸው ደረሰ:: በጊዜው ብዙ ሰው
በሰማዕትነት አለፈ:: አባ ኦሪም ወደ #ቤተ_እግዚአብሔር
ገብተው ስለ ራሳቸውና ሕዝቡ ጽናትን: ደኅንነትን ለመኑና
ከቤተ ክርስቲያን ወጡ::
በቀጥታ የሔዱትም ወደ #ዐውደ_ስምዕ (የምሥክርነት
አደባባይ) ነበር:: በመኮንኑ ፊት ቀርበው "#ክርስቶስ
አምላክ: ፈጣሪ: የሁሉ ጌታ ነው:: የእናንተ ጣዖት ግን
ጠፊ: ረጋፊ: ወርቅ: ብር: እንጨትና ድንጋይ ነው" ሲሉ
በድፍረት ተናገሩ:: መኮንኑም ከአነጋገራቸው የተነሳ ተቆጥቶ ሥቃይን አዘዘባቸው:: ወታደሮቹ ይሆናል ያሉትን ማሰቃያ ሁሉ
#አባ_ኦሪ ላይ ሞከሩ:: በሁዋላም ወደ ጨለማ እሥር
ቤት ወስደው ጣሏቸው:: በእሥር ቤት ውስጥም ድውያንን ፈወሱ: ተአምራትን ሠሩ:: ይሕንን ዜና የሰሙ አሕዛብ ብዙ ድውያንን ሰብስበው መጡ:: ቅዱሱም ሁሉን በጸሎታቸው ፈወሱ:: በዚህ
ምክንያትም ብዙ አሕዛብ ወደ ክርስትና መጥተዋል::
በክርስቶስ አምነውም ለክብር በቅተዋል:: ቅዱሱንም ከእሥር ቤት አውጥተው ብዙ ካሰቃዩዋቸው በሁዋላ በዚህች ቀን ገድለዋቸው ሰማዕትነትን
አግኝተዋል:: #በአክሊለ_ጽድቅ ላይ #አክሊለ_ካህናትን :
#በአክሊለ_ካህናትም ላይ #አክሊለ_ሰማዕታትን
ደርበዋል::
#አምላከ_ቅዱሳን_በአባቶቻችን_ጽናት_ያጽናን::_ጸጋ_በረከታቸውንም_ይክፈለን::
✞✞✞ እንኩዋን ለካህኑ #ሰማዕት_አባ_ኦሪ ዓመታዊ
የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞✞✞
#ቅዱስ_አባ_ኦሪ_ቀሲስ "
ይህ ቅዱስ አባት የዘመነ ሰማዕታት ፍሬ ነው:: በዘመኑ
(በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን) #ክርስቲያን መሆን ብቻውን
ለሞት እንደሚያበቃ ወንጀል ይቆጠር ነበር:: በጊዜው
ክርስቲያን ከመሆን በባሰ መንገድ #እረኛ_ካህን ሆኖ
መገኘት በጣም ከባድ ነበር::
ከመነሻውም ያን ጊዜ ክህነት የሚሰጠው በሕዝቡና
በሊቀ ዻዻሱ ምርጫ ነበር እንጂ እንደ ዘንድሮ "እኔን ሹሙኝ" ማለት ልማድ አልነበረም:: ምዕመናንም
እረኛቸውን ሲመርጡ በጉቦ: በዝምድና አይደለም::
በርትቶ የሚያበረታቸውን: ለመንጋው ራሱን አሳልፎ
የሚሰጠውን ይመርጣሉ እንጂ::
ያልሆነ ሰው ለክህነት ቢመረጥ አንድም ክዶ ያስክዳል:
ሲቀጥልም ለሕዝቡ መሰናክል መሆኑ አይቀርም::
በጊዜው ( #በዘመነ_ሰማዕታት ) የነበሩ ካህናት የቤት
ሥራቸውም ማስተማር ብቻ አልነበረም:: በድፍረት
በምዕመናን ፊት አንገታቸውን ለሰይፍ መስጠት
ይጠበቅባቸው ነበር እንጂ::
ይህንን በገሃድ መፈጸም ከቻሉ አበው አንዱ ደግሞ አባ
ኦሪ ቀሲስ ናቸው:: ቅዱሱ ተወልደው ባደጉባት ሃገረ
#ስጥኑፍ (የግብጽ አውራጃ ናት) መጻሕፍትን የተማሩ:
ተወዳጅ እና ደግ ሰው ነበሩ::
አባ ኦሪ ገና ከወጣትነት ቀዳሚ ግብራቸው መንኖ
ጥሪት (ምናኔ) ነበር:: በንጽሕናቸው ደስ የተሰኙ
ምዕመናንም "ቅስና ተሹመህ ምራን: አስተምረን"
ቢሏቸው አበው ውዳሴ ከንቱን አይፈልጉምና "አይሆንም" አሉ::
ነገሩ ፈቃደ እግዚአብሔር ነበረና አባ ኦሪ ቅስናን ተሹመው ያገለግሉ ገቡ:: ሕዝቡን በማስተማር:
በመምከር: ደካማውን በማጽናት ብዙ ደክመዋል:: ከቅድስናቸው የተነሳ ቅዳሴ ሊቀድሱ ሲገቡ #ጌታችን በገሃድ ይገለጥላቸው ነበር:: ሠራዊተ መላእክትም
ከበው ይነጋገሯቸው ነበር::
#ሥጋውን_ደሙን በማቀበልም ተግተው ዘመናት
አለፉ:: ቆይቶ ግን ያ በዜና ይሰሙት የነበረ መከራ
( #ሰማዕትነት ) በደጃቸው ደረሰ:: በጊዜው ብዙ ሰው
በሰማዕትነት አለፈ:: አባ ኦሪም ወደ #ቤተ_እግዚአብሔር
ገብተው ስለ ራሳቸውና ሕዝቡ ጽናትን: ደኅንነትን ለመኑና
ከቤተ ክርስቲያን ወጡ::
በቀጥታ የሔዱትም ወደ #ዐውደ_ስምዕ (የምሥክርነት
አደባባይ) ነበር:: በመኮንኑ ፊት ቀርበው "#ክርስቶስ
አምላክ: ፈጣሪ: የሁሉ ጌታ ነው:: የእናንተ ጣዖት ግን
ጠፊ: ረጋፊ: ወርቅ: ብር: እንጨትና ድንጋይ ነው" ሲሉ
በድፍረት ተናገሩ:: መኮንኑም ከአነጋገራቸው የተነሳ ተቆጥቶ ሥቃይን አዘዘባቸው:: ወታደሮቹ ይሆናል ያሉትን ማሰቃያ ሁሉ
#አባ_ኦሪ ላይ ሞከሩ:: በሁዋላም ወደ ጨለማ እሥር
ቤት ወስደው ጣሏቸው:: በእሥር ቤት ውስጥም ድውያንን ፈወሱ: ተአምራትን ሠሩ:: ይሕንን ዜና የሰሙ አሕዛብ ብዙ ድውያንን ሰብስበው መጡ:: ቅዱሱም ሁሉን በጸሎታቸው ፈወሱ:: በዚህ
ምክንያትም ብዙ አሕዛብ ወደ ክርስትና መጥተዋል::
በክርስቶስ አምነውም ለክብር በቅተዋል:: ቅዱሱንም ከእሥር ቤት አውጥተው ብዙ ካሰቃዩዋቸው በሁዋላ በዚህች ቀን ገድለዋቸው ሰማዕትነትን
አግኝተዋል:: #በአክሊለ_ጽድቅ ላይ #አክሊለ_ካህናትን :
#በአክሊለ_ካህናትም ላይ #አክሊለ_ሰማዕታትን
ደርበዋል::
#አምላከ_ቅዱሳን_በአባቶቻችን_ጽናት_ያጽናን::_ጸጋ_በረከታቸውንም_ይክፈለን::