ግጥም ሲጥም - Gitem Sitem
1.85K subscribers
842 photos
55 videos
20 files
394 links
የዘመናችንን ቀለም ያሳያሉ ያልናቸውን የዚህ ትውልድ የስነ ግጥም ውጤቶችን እንጋራ - እናጋራ።
ለማካፈል የፈለጋችሁትን በGitem_Sitem ፣ gitemsitem@gmail.com የጸሃፊ ስም እና ርዕስ አክላችሁ ላኩልን።

We are all about sharing this generation's poetry. Please email us your pieces gitemsitem@gmail.com
Download Telegram
May the new year brings us more joy, peace, unity and creativity!!

Happy new year everyone

#tba #tibebbeadebabay #digitalart #digitalartfestival #artinaddis
Forwarded from Tibeb Be Adebabay-TBA
ይህችን ጣፋጭ ግጥም ከግጥም ሲጥም ያጣጥሙልን
የግጥም ሲጥም አባል ከሆነው ቶማስ አድማሱ

እኔ ፀሐይ

እሰይ አደይ ፈነዳች፤
የመስከረም ፀሐይ ወጣች፤
አበባየሁ አሉ ልጆች፤
አበባ ያልያዙ እጆች፤
በምርቃት ሊወለዱ 30 እና 60 ጥጆች፤
ቀልዬ ከሶሪት ላባ፤
ካባቴ ገቦ ወጥቼ ከናቴ ማ'ጸን ስገባ፤
ይኸው መስከረም ጠባ።
እልል አበብሽ ብዬ
ለምለም አደይ ነቅዬ፤
እንግጫሽ አበባ፤አበባየሽ ለምለም
የመስከረም ጸሐይ ወጣች
ከእንዲህ ነጎድጓድ መፍራት በሰማይ ማማረር የለም።
በክረምት ጠል ርሶ፤ ሊመጣ ጸደይ ያማረ፤
በምርቃት ወንድ ሊሰጥ በሴት አካል ወንድ አደረ።
አበባ ነኝ እኔ አበባ
ከአድማስ ፀሐይ ሳትገባ
መታፈር በከንፈር ያልኩ ጥርሴ መንታ የሚያነባ
ቢጫነት በሆዴ ያለ ልቤ መዓት የሚያደባ፤
አበባ ነኝ እኔ አበባ።
ለወደድኩት የዓይን ጥም
ከካህን ማስር ምፈታ ከደብተራ ምጠመጥም
የጠላሁት የሚሰጥም
ለተናቀ ረባዳ
ለተከበረ ሰው ሜዳ።
አበባ ነኝ እኔ አበባ።
እሰይ አደይ ፈነዳች፤ ይኸው ጳጉሜ ከነዳች።
ከሰማይ ምንም ሳይጎድል ከመሬት ሳይጨምር አንዳች።
(ቶ)በምን አገባኝ ፍካሬ አክናፌን ስዘረጋጋ
(ማ) ነህ ብሎ ለሚያዛጋ
(ስ)ብዬ አፉን የማሲዝ የማልፈጥን የማልረጋ።
መሬት ቢጫ ስትለብስ። የአምናን መከራ አልፌ
እልል የምል ችቦ ወገብ ተደግፌ
ለከርሞ ትልሜን ለፍፌ
የሚል ግጥም ሳሰናዳ
እሰይ አደይ ፈነዳ::

#gitemsitem #tibebbeadebabay #tba

ይከታተሉን
ቴሌግራም: t.me/Tibeb_Be_Adebabay

ፌስቡክ: facebook.com/Tibeb2020

ትዊተር: twitter.com/TibebBe

ዮቲዩብ: youtube.com/channel/UCmvDcNWiv8oNpzL7elz1fag

ዌብሳይት: tibebbeadebabay.org