የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ከአዲስ አበባ ሴቶች ፤ ሕጻናት እና መሕበራዊ ጉዳይ ቢሮ ጋር በቅንጅት በመስራቱ እውቅና ተሰጠው።
የአ.አ.ሴ.ሕ.ማ.ጉ.ቢሮ በ2017 በጀት ዓመት በቅንጅት ለመስራት ያቀዳቸው ተግባራት አፈፃፀምና እና በ2018 በጀት ዓመት በቅንጅት ለመስራት ባቀዳቸው ተግባራት ላይ በቅንጅት ከሚሰሩት ሴክተሮች ጋር የግምገማ ውይይት አድርጓል፡፡
የቅንጅት አሰራር እቅድ አፈፃፀም ግምገማውን የመሩት የቢሮው ኃላፊ ወ/ሮ ቆንጂት ደበላ በበጀት ዓመቱ አቅደን ላሳካናቸው ዘርፍ ተሻጋሪ ተግባራት በቅንጅት አብረውን የሰሩ ሴክተሮች የጎላ ሚና ተወጥተዋል ሲሉ ገልፀዋል፡፡
ቢሮ ኃላፊዋ አክለውም ቢሮው በአብዛኛው ስራዎቹ ዘርፍ ተሻጋሪ በመሆናቸው ከሚመለከታቸው ሴክተር ተቋማት ጋር በቅንጅት አቅዶ መስራትን በልዩ ትኩረት እየሰራበት እንደሚገኝና አጠናክሮ እንደሚቀጥልበት ተናግረዋል፡፡
በቅንጅታዊ አሰራር የእቅድ አፈፃፀም እና የቀጣይ እቅድ ያቀረቡት የቢሮው የስታንዳርዳይዘሽን ዝግጅት እና አገልግሎት አሰጣጥ ክትትልና ድጋፍ ዳይሬክተር አቶ ዮናስ ሲሳይ በቅንጅት የሚሰሩ ተግባራት አፈፃፀም ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ መምጣቱን ጠቅሰው፤ በቀጣይ በሁሉም ተግባራት የላቀ ውጤት ለማስመዝገብ በርብርብ መስራት ይጠበቅብናል ብለዋል፡፡
በመድረኩ የአዲስ አበባ ሐይማኖት ተቋማት ጉባኤን በመወከል የሴቶች እና ወጣቶች መምሪያ ሃላፊ ወ/ሮ ራምላ ከድር የተሳተፉ ሲሆን የሴክተር ተቋማት አመራሮችና ተወካዮች ቢሮው ለቅንጅትዊ አሰራር የሰጠው ትኩረት በጋራ የሚሰሩ ስራዎች በተሳካ ሁኔታ እንዲፈፀሙ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ገልፀው፤ ለ2018 በጀት ዓመት የታቀዱ ተግባራት ለማሳካት በተሻለ ርብርብ እና መናበብ እንደሚሰሩ አስተያየቶቻቸውን ሰጥተዋል፡፡
በግምገማዊ ውይይቱ ሴክተሮች በ2017 በጀት ዓመት የእቅድ አፈፃፀም በነበራቸው ተሳትፎና አፈፃፀም ልክ በጣም ከፍተኛ፣ ከፍተኛና አጥጋቢ በሚል የእውቅናና ምስጋና ሰርተፍኬት ተበርክቶላቸዋል፡፡
መረጃው የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ነው።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ ቤተልሔም ደረጄ
የአ.አ.ሴ.ሕ.ማ.ጉ.ቢሮ በ2017 በጀት ዓመት በቅንጅት ለመስራት ያቀዳቸው ተግባራት አፈፃፀምና እና በ2018 በጀት ዓመት በቅንጅት ለመስራት ባቀዳቸው ተግባራት ላይ በቅንጅት ከሚሰሩት ሴክተሮች ጋር የግምገማ ውይይት አድርጓል፡፡
የቅንጅት አሰራር እቅድ አፈፃፀም ግምገማውን የመሩት የቢሮው ኃላፊ ወ/ሮ ቆንጂት ደበላ በበጀት ዓመቱ አቅደን ላሳካናቸው ዘርፍ ተሻጋሪ ተግባራት በቅንጅት አብረውን የሰሩ ሴክተሮች የጎላ ሚና ተወጥተዋል ሲሉ ገልፀዋል፡፡
ቢሮ ኃላፊዋ አክለውም ቢሮው በአብዛኛው ስራዎቹ ዘርፍ ተሻጋሪ በመሆናቸው ከሚመለከታቸው ሴክተር ተቋማት ጋር በቅንጅት አቅዶ መስራትን በልዩ ትኩረት እየሰራበት እንደሚገኝና አጠናክሮ እንደሚቀጥልበት ተናግረዋል፡፡
በቅንጅታዊ አሰራር የእቅድ አፈፃፀም እና የቀጣይ እቅድ ያቀረቡት የቢሮው የስታንዳርዳይዘሽን ዝግጅት እና አገልግሎት አሰጣጥ ክትትልና ድጋፍ ዳይሬክተር አቶ ዮናስ ሲሳይ በቅንጅት የሚሰሩ ተግባራት አፈፃፀም ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ መምጣቱን ጠቅሰው፤ በቀጣይ በሁሉም ተግባራት የላቀ ውጤት ለማስመዝገብ በርብርብ መስራት ይጠበቅብናል ብለዋል፡፡
በመድረኩ የአዲስ አበባ ሐይማኖት ተቋማት ጉባኤን በመወከል የሴቶች እና ወጣቶች መምሪያ ሃላፊ ወ/ሮ ራምላ ከድር የተሳተፉ ሲሆን የሴክተር ተቋማት አመራሮችና ተወካዮች ቢሮው ለቅንጅትዊ አሰራር የሰጠው ትኩረት በጋራ የሚሰሩ ስራዎች በተሳካ ሁኔታ እንዲፈፀሙ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ገልፀው፤ ለ2018 በጀት ዓመት የታቀዱ ተግባራት ለማሳካት በተሻለ ርብርብ እና መናበብ እንደሚሰሩ አስተያየቶቻቸውን ሰጥተዋል፡፡
በግምገማዊ ውይይቱ ሴክተሮች በ2017 በጀት ዓመት የእቅድ አፈፃፀም በነበራቸው ተሳትፎና አፈፃፀም ልክ በጣም ከፍተኛ፣ ከፍተኛና አጥጋቢ በሚል የእውቅናና ምስጋና ሰርተፍኬት ተበርክቶላቸዋል፡፡
መረጃው የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ነው።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ ቤተልሔም ደረጄ
👍2
በኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን የደቡብ ምስራቅ ክልል የባሌ ጎባ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን 50ኛ የወርቅ ኢዩቤልዩ በዓል በደመቀ ሁኔታ ተከበረ።
"ዘመን ተሻጋሪ የወንጌል የማዳን ሃይል” በሚል መሪ ቃል የቤተክርስቲያኒቱ ምስረታ 50ኛ የወርቅ ኢዩቤልዩ ሲከበር የቤተ እምነቱ ም/"ፕሬዝዳንት መጋቢ ለወየሁ ስንሻው፣ ከአዲስ አበባ፣ ከአዳማ፣ ከሀዋሳ ከአሜሪካ የተለያዩ ግዛቶች የመጡ ቀደምት የቤተክርስቲያኒቱ አባላትና አገልጋዮች ተገኝተዋል፡፡
የኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን ም/ፕሬዝዳንት የሆኑት መጋቢ ለወየሁ ስንሻው በበኩላቸው የጎባ ሙሉ ወንጌል ቤ/ክ ከራሷ አልፋ በሀገርና በዓለም አቀፍ ደረጃ ተጽዕኖ ፈጣሪ የሆኑ አገልጋዮችን አፍርታ ሰጥታናለች በማለት ካመሰገኑ በኋላ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸዉን አስተላልፈዋል።
በበዓሉ ላይም በ1966 ዓ.ም ለመጀመሪያ ጊዜ ወንጌልን የሰበኩትና የአሁኑ የኢ/ወ/አ/ክ/ህ ፕሬዝዳንት የሆኑት መጋቢ ጻዲቁ አብዶ የእግዚአብሔርን ቃል ሰብከዋል፡፡ እንዲሁም ከመጋቢ ጻዲቁ ጋር ከጅማሬው ጀምሮ አብሮ ወንጌልን የሰበኩትና አሁን የአይ ኤል አይ መስራችና መሪ የሆነት ፕሮፌሰር ባደግ በቀለ የእግዚአብሔርን ቃል በማካፈል አገልግለዋል፡፡
የጎባ ሙሉ ወንጌል "ሀ" መዘምራን የመዝሙር አልበማቸዉን ከማስመረቅ በተጨማሪ በበዓሉ ላይ በዝማሬ አገልግለዋል፡፡ በዓል ላይ የጎባ ክ/ከተማ ም/አስተዳዳሪ ተገኝተው የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።በመጨረሻም የቤ/ክ የመሪዎች ጉባዔ ሰብሳቢ የሆኑት አቶ ሀይሉ ንባቢ በተለያየ መንገድ ለበዓሉ መሳካት አስተዋጽኦ ያደረጉትን ሁሉ አመስግነው በዓሉ ለታላቅ ደስታና መጽናናት እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።
መረጃው የኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን ነው።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፤ ቤተልሔም ደረጄ
"ዘመን ተሻጋሪ የወንጌል የማዳን ሃይል” በሚል መሪ ቃል የቤተክርስቲያኒቱ ምስረታ 50ኛ የወርቅ ኢዩቤልዩ ሲከበር የቤተ እምነቱ ም/"ፕሬዝዳንት መጋቢ ለወየሁ ስንሻው፣ ከአዲስ አበባ፣ ከአዳማ፣ ከሀዋሳ ከአሜሪካ የተለያዩ ግዛቶች የመጡ ቀደምት የቤተክርስቲያኒቱ አባላትና አገልጋዮች ተገኝተዋል፡፡
የኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን ም/ፕሬዝዳንት የሆኑት መጋቢ ለወየሁ ስንሻው በበኩላቸው የጎባ ሙሉ ወንጌል ቤ/ክ ከራሷ አልፋ በሀገርና በዓለም አቀፍ ደረጃ ተጽዕኖ ፈጣሪ የሆኑ አገልጋዮችን አፍርታ ሰጥታናለች በማለት ካመሰገኑ በኋላ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸዉን አስተላልፈዋል።
በበዓሉ ላይም በ1966 ዓ.ም ለመጀመሪያ ጊዜ ወንጌልን የሰበኩትና የአሁኑ የኢ/ወ/አ/ክ/ህ ፕሬዝዳንት የሆኑት መጋቢ ጻዲቁ አብዶ የእግዚአብሔርን ቃል ሰብከዋል፡፡ እንዲሁም ከመጋቢ ጻዲቁ ጋር ከጅማሬው ጀምሮ አብሮ ወንጌልን የሰበኩትና አሁን የአይ ኤል አይ መስራችና መሪ የሆነት ፕሮፌሰር ባደግ በቀለ የእግዚአብሔርን ቃል በማካፈል አገልግለዋል፡፡
የጎባ ሙሉ ወንጌል "ሀ" መዘምራን የመዝሙር አልበማቸዉን ከማስመረቅ በተጨማሪ በበዓሉ ላይ በዝማሬ አገልግለዋል፡፡ በዓል ላይ የጎባ ክ/ከተማ ም/አስተዳዳሪ ተገኝተው የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።በመጨረሻም የቤ/ክ የመሪዎች ጉባዔ ሰብሳቢ የሆኑት አቶ ሀይሉ ንባቢ በተለያየ መንገድ ለበዓሉ መሳካት አስተዋጽኦ ያደረጉትን ሁሉ አመስግነው በዓሉ ለታላቅ ደስታና መጽናናት እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።
መረጃው የኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን ነው።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፤ ቤተልሔም ደረጄ