የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የነበረው አራተኛው አገር አቀፍ የሰላም ኮንፍረንስ በድምቀት ተጠናቀቀ፡፡
የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ከሐረሪ ክልል የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጋር በመተባበር ለሁለት ቀናት በሐረሪ ክልል፣ ሐረር ከተማ ላይ ሲያካሂደው የነበረው አገር አቀፍ የሰላም ኮንፍረንስ በድምቀት ተጠናቋል፡፡
በሰላም ኮንፍረንሱ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ጸሐፊ ሊቀ ትጉኃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ ባስተላለፉት የሰላም መልዕክት የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ አለመግባባቶችን እና ግጭቶችን ለመፍታት የሚረዱ በርካታ የውይይት መድረኮች በማዘጋጀት፣ ችግሮች የሚፈቱበትን የጋራ የመፍትሄ አቅጣጫ በማስቀመጥ አለመግባባቶች እንዲፈቱ እያደረገ ያለው ጥረት ተጨባጭ ለውጥ እያመጣ ነው ሲሉ ተናግረዋል።
ጠቅላይ ጸኃፊው አክለውም የእርስ በእርስ ግንኙነትን የሚያጠናክሩ በተለይም መከባበርን፣ ሰላምን፣ አብሮነትን እና ይቅርታን የሚያጎለብቱ በረካታ ተግባራት መከናወናቸውን በመግለጽ የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ ይቻል ዘንድ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ሰላምን ከመገንባት አንፃር ኃላፊነታቸውን ከምን ጊዜውም በላይ እንዲወጡ አደራ ብለዋል፡፡
በተያያዘም የሀገራችን ሰላም እንዲጸና የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ እንዲሁም በተለያዩ አካባቢዎች በግጭት ውስጥ ለሚገኙ አካላት በሰላም በመነጋገር ችግሮቻቸውን እንዲፈቱ የሰላም ጥሪ በአክብሮት ያቀርባል በማለት በድጋሚ የሰላም ጥሪ አቅርበዋል፡፡
በሰላም ኮንፍረንስ መድረክ ላይ በክብር እንግዳነት የተገኙት የሀረሪ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ክብርት ወ/ሮ ሮዛ ኡመር እንደተናገሩት ሀረር ከአንድ ሺህ ዓመት በፊት ጀምሮ የተለያዩ ብሔር ብሔረሰቦች፣ የተለያዩ የሃይማኖቶች ተቋማት እና ተከታዬቻቸው ተቻችለው እና ተከባብረው በፍቅር የሚኖርባት የሰላም፣ የመቻቻል እና የአብሮነት ተምሳሌት የሆነች ድንቅ ከተማ መሆኗን አስታውሰዋል።
ክብርት ም/ርዕሰ መስተዳድርዋ አክለውም የሃይማኖት ተቋማት ለሰላም ግንባታ እያበረከቱት ያለው አስተዋፅኦ እጅግ የላቀ መሆኑን በመጠቆም የሃይማኖት ተቋማት በሀገራችን ኢትዮጵያ ሰላምን ይበልጥ ለማስረፅ እና ለመገንባት የሚያደርጉትን ጥረት አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጠይቀዋል።
የኢፌድሪ የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ የሆኑት ክቡር ዶክተር ካይረዲን ተዘራ (ዶ/ር) በበኩላቸው የሃይማኖት ተቋማት በሀገር ደረጃ ዘላቂ እና አስተማማኝ ሰላም ለመገንባት የሚያደርጉት ጥረት እና አስተዋጽዎ ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመው በቀጣይም ይህን የጀመሩትን ታላቅ የሰላም ግንባታ ሥራ በመቀናጀት አጠናክረው እንዲቀጥሉ የአደራ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
ክቡር ሚኒስትሩ አክለውም የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ አባል የሃይማኖት ተቋማቱን በማስተባበር እና በማቀናጀት ሰላምን ለማጽናት የሚያደርገውን ጥረት አድንቀው በቀጣይም የሃይማኖት ተቋማቱን ትብብር ይበልጥ በማጎልበት የጀመራቸውን የሰላም ግንባታ ሥራዎች እንዲያስቀጥል ጠይቀዋል፡፡
የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ከሐረሪ ክልል የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጋር በመተባበር ባዘጋጀው አራተኛው አገር አቀፍ ሕዝባዊ የሰላም ኮንፍረንስ ላይ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ አምስተኛውን አገር አቀፍ የሰላም ኮንፍረንስ እንዲያዘጋጅ መመረጡ በይፋ የተበሰረ ሲሆን የሐረሪ ክልል የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤም ለአምስተኛው አገር አቀፍ የሰላም ኮንፍረስ አዘጋጀ ሆኖ ለተመረጠው የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የሰላም ዋንጫውን በክብር አስረክቧል፡፡
መረጃውን ከኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ አገኘነው።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ ቤተልሔም ደረጄ
የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ከሐረሪ ክልል የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጋር በመተባበር ለሁለት ቀናት በሐረሪ ክልል፣ ሐረር ከተማ ላይ ሲያካሂደው የነበረው አገር አቀፍ የሰላም ኮንፍረንስ በድምቀት ተጠናቋል፡፡
በሰላም ኮንፍረንሱ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ጸሐፊ ሊቀ ትጉኃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ ባስተላለፉት የሰላም መልዕክት የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ አለመግባባቶችን እና ግጭቶችን ለመፍታት የሚረዱ በርካታ የውይይት መድረኮች በማዘጋጀት፣ ችግሮች የሚፈቱበትን የጋራ የመፍትሄ አቅጣጫ በማስቀመጥ አለመግባባቶች እንዲፈቱ እያደረገ ያለው ጥረት ተጨባጭ ለውጥ እያመጣ ነው ሲሉ ተናግረዋል።
ጠቅላይ ጸኃፊው አክለውም የእርስ በእርስ ግንኙነትን የሚያጠናክሩ በተለይም መከባበርን፣ ሰላምን፣ አብሮነትን እና ይቅርታን የሚያጎለብቱ በረካታ ተግባራት መከናወናቸውን በመግለጽ የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ ይቻል ዘንድ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ሰላምን ከመገንባት አንፃር ኃላፊነታቸውን ከምን ጊዜውም በላይ እንዲወጡ አደራ ብለዋል፡፡
በተያያዘም የሀገራችን ሰላም እንዲጸና የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ እንዲሁም በተለያዩ አካባቢዎች በግጭት ውስጥ ለሚገኙ አካላት በሰላም በመነጋገር ችግሮቻቸውን እንዲፈቱ የሰላም ጥሪ በአክብሮት ያቀርባል በማለት በድጋሚ የሰላም ጥሪ አቅርበዋል፡፡
በሰላም ኮንፍረንስ መድረክ ላይ በክብር እንግዳነት የተገኙት የሀረሪ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ክብርት ወ/ሮ ሮዛ ኡመር እንደተናገሩት ሀረር ከአንድ ሺህ ዓመት በፊት ጀምሮ የተለያዩ ብሔር ብሔረሰቦች፣ የተለያዩ የሃይማኖቶች ተቋማት እና ተከታዬቻቸው ተቻችለው እና ተከባብረው በፍቅር የሚኖርባት የሰላም፣ የመቻቻል እና የአብሮነት ተምሳሌት የሆነች ድንቅ ከተማ መሆኗን አስታውሰዋል።
ክብርት ም/ርዕሰ መስተዳድርዋ አክለውም የሃይማኖት ተቋማት ለሰላም ግንባታ እያበረከቱት ያለው አስተዋፅኦ እጅግ የላቀ መሆኑን በመጠቆም የሃይማኖት ተቋማት በሀገራችን ኢትዮጵያ ሰላምን ይበልጥ ለማስረፅ እና ለመገንባት የሚያደርጉትን ጥረት አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጠይቀዋል።
የኢፌድሪ የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ የሆኑት ክቡር ዶክተር ካይረዲን ተዘራ (ዶ/ር) በበኩላቸው የሃይማኖት ተቋማት በሀገር ደረጃ ዘላቂ እና አስተማማኝ ሰላም ለመገንባት የሚያደርጉት ጥረት እና አስተዋጽዎ ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመው በቀጣይም ይህን የጀመሩትን ታላቅ የሰላም ግንባታ ሥራ በመቀናጀት አጠናክረው እንዲቀጥሉ የአደራ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
ክቡር ሚኒስትሩ አክለውም የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ አባል የሃይማኖት ተቋማቱን በማስተባበር እና በማቀናጀት ሰላምን ለማጽናት የሚያደርገውን ጥረት አድንቀው በቀጣይም የሃይማኖት ተቋማቱን ትብብር ይበልጥ በማጎልበት የጀመራቸውን የሰላም ግንባታ ሥራዎች እንዲያስቀጥል ጠይቀዋል፡፡
የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ከሐረሪ ክልል የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጋር በመተባበር ባዘጋጀው አራተኛው አገር አቀፍ ሕዝባዊ የሰላም ኮንፍረንስ ላይ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ አምስተኛውን አገር አቀፍ የሰላም ኮንፍረንስ እንዲያዘጋጅ መመረጡ በይፋ የተበሰረ ሲሆን የሐረሪ ክልል የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤም ለአምስተኛው አገር አቀፍ የሰላም ኮንፍረስ አዘጋጀ ሆኖ ለተመረጠው የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የሰላም ዋንጫውን በክብር አስረክቧል፡፡
መረጃውን ከኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ አገኘነው።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ ቤተልሔም ደረጄ
የኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን ዋና ፅ/ቤት ፣ የልማት ኮሚሽኑ ዋና መ/ቤት እና የሴሚናሪው ሰራተኞች በጋራ በአዳማ ከተማ ለሁለት ቀናት ልዩ የአንድነትና የጸሎት መንፈሳዊ ፕሮግራም አካሄዱ።
ሐምሌ 28 እና 29 /2017 ዓ.ም በአዳማ በተካሄው የአንድነትና የጸሎት ፕሮግራም ላይ የቤተ ክርስቲያኒቱ ፕረዚዳንት መጋቢ ላኮ በዳሶ ፣ም/ፕረዚዳንት መጋቢ ለወየሁ ስንሻው ፣የልማት ኮሚን ኮሚሽነር መጋቢ ብርሃኑ ታረቀኝ ፣የሴሚናሪው ፕረዚዳንት መምህር ሂሩህ አድማሱ እና ሁሉም ሰራተኞች ተገኝተዋል ።
ፕሮግራሙም ጾም ጸሎት፣ አምልኮ፣ የተሃድሶ እና የመነቃቃት ትምርህት እና የአንድነት ፕሮግራምን ያካተተ ነበር።
ለጉባኤው መንፈሳዊ ሰላምታ በማቅረብ ፕሮግራሙን በጸሎት ያስጀመሩት መጋቢ ብርሃን ታረቀኝ ሲሆኑ መጋቢ ላኮ በዳሶ " እምነት ተስፋ ፍቅርን እንያዝ" በሚል ርዕስ የእግዚአብሔርን ቃል መልዕክት ለጉባኤው አካፍለዋል። መጋቢ ለወየሁ ስንሻውም እግዚአብሔር ምድራችንን ኢትዮጵያ እንዲጎበኛት እና እንዲባርካት ጸሎት አድርገዋል።
የአንድነት እና የጸሎት ፕሮግራሙን የተዘጋጀበትን አላማ ሲያሳውቁ የልማት ኮሚሽኑ ኮሚሽነር የሆኑትን መጋቢ ብርሃኑ ታረቀኝ "ዋነኛ ያሰባሰበን የእግዚአብሔር መንግስት ጉዳይ እና በአንድነት ህበረታችንን እንዲጠናከር ነው።” በማለት ተናግረዋል።
አክለውም “በፊቱ ጸልየናል ፣ተመካክረናል ፣ እንዲሁም አመቱን በሙሉ የረዳንን ጌታን አመስግነናል። ራሳችንምም በማየት ለቀጣይ አዲስ አመት በታደሰ ሀይል አገልግሎታችን እንዲሰምር መንፈስ ቅዱስ ምሪትና ሀይል ሰጥቶናል። ከጠበቅነው በላይ ጌታ ረድቶናል።” ብለዋል።
በፕሮግራሙ የተሳተፉ ወገኖች ጌታ መልካም የአንድነት ጊዜ እንደሰጣቸው ገልጾዋል።
መረጃውን ከኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን አገኘነው።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ ቤተልሔም ደረጄ
ሐምሌ 28 እና 29 /2017 ዓ.ም በአዳማ በተካሄው የአንድነትና የጸሎት ፕሮግራም ላይ የቤተ ክርስቲያኒቱ ፕረዚዳንት መጋቢ ላኮ በዳሶ ፣ም/ፕረዚዳንት መጋቢ ለወየሁ ስንሻው ፣የልማት ኮሚን ኮሚሽነር መጋቢ ብርሃኑ ታረቀኝ ፣የሴሚናሪው ፕረዚዳንት መምህር ሂሩህ አድማሱ እና ሁሉም ሰራተኞች ተገኝተዋል ።
ፕሮግራሙም ጾም ጸሎት፣ አምልኮ፣ የተሃድሶ እና የመነቃቃት ትምርህት እና የአንድነት ፕሮግራምን ያካተተ ነበር።
ለጉባኤው መንፈሳዊ ሰላምታ በማቅረብ ፕሮግራሙን በጸሎት ያስጀመሩት መጋቢ ብርሃን ታረቀኝ ሲሆኑ መጋቢ ላኮ በዳሶ " እምነት ተስፋ ፍቅርን እንያዝ" በሚል ርዕስ የእግዚአብሔርን ቃል መልዕክት ለጉባኤው አካፍለዋል። መጋቢ ለወየሁ ስንሻውም እግዚአብሔር ምድራችንን ኢትዮጵያ እንዲጎበኛት እና እንዲባርካት ጸሎት አድርገዋል።
የአንድነት እና የጸሎት ፕሮግራሙን የተዘጋጀበትን አላማ ሲያሳውቁ የልማት ኮሚሽኑ ኮሚሽነር የሆኑትን መጋቢ ብርሃኑ ታረቀኝ "ዋነኛ ያሰባሰበን የእግዚአብሔር መንግስት ጉዳይ እና በአንድነት ህበረታችንን እንዲጠናከር ነው።” በማለት ተናግረዋል።
አክለውም “በፊቱ ጸልየናል ፣ተመካክረናል ፣ እንዲሁም አመቱን በሙሉ የረዳንን ጌታን አመስግነናል። ራሳችንምም በማየት ለቀጣይ አዲስ አመት በታደሰ ሀይል አገልግሎታችን እንዲሰምር መንፈስ ቅዱስ ምሪትና ሀይል ሰጥቶናል። ከጠበቅነው በላይ ጌታ ረድቶናል።” ብለዋል።
በፕሮግራሙ የተሳተፉ ወገኖች ጌታ መልካም የአንድነት ጊዜ እንደሰጣቸው ገልጾዋል።
መረጃውን ከኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን አገኘነው።
ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ ቤተልሔም ደረጄ